ማስታወቂያ
በጎርጎሪዮሳዊው የዘመን አቆጣጠር ማርች ማለትም መጋቢት ወር በዓለም አቀፍ ደረጃ ስለአንጀት ካንሰር የግንዛቤ ማስጨበጫ እንቅስቃሴ የሚከናወንበት ወር ነው። የአንጀት ካንሰር በመላው ዓለም በካንሰር ምክንያት ከሚከሰተው ሞት በሁለተኛ ደረጃ እንደሚገኝ የዓለም የጤና ድርጅት መረጃ ያመለክታል። የዘርፉ ሀኪሞች ሰዎች የካንሰር ምልክቶችን አስቀድመው በመረዳት ስር ከመስደዱ አስቀድሞ ወደ ህክምና እንዲሄዱና አስፈላጊውን ክትትል እንዲያደርጉ ይመክራሉ።