1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል
ውዝግቦችአፍሪቃ

በሱዳን የርስ በርስ ጦርነት የፈጠረው አስከፊ ርሀብ

Gebeyaw Nigusseሰኞ፣ መጋቢት 30 2016

https://p.dw.com/p/4eYKb

የሱዳን ጦርነት ባጭር ጊዜ ውስጥ በሰፊው በመሰራጨትና በርካታ ሚሊዮንችም በማፈናቀልና እንዲሰደዱ በማድረግ በቀዳሚነት የሚጠቀስ ሁኗል። ሆኖም ግን፤ ብዙ ሽፋን እንዳልተሰጠውና ጦርነቱን ለማስቆምም አቅሙና ችሎታው ካላቸው ወገኖች ብዙም ፍላጎት እንዳልታየ ነው ታዛቢዎች የሚናገሩት። ሁለቱም ወገኖች ያለ ሌላ ሦስተኛ ወገን ድጋፍ ጦረነቱን ለማስጀመርም ሆነ ለማስቀጠል አይችሉም ነበር የሚሉት እነዚሁ ታዛቢዎች፤ የቅርብም ሆነ የሩቅ ግን አቅሙ ያላቸው መንግሥታት ይልቁንም ሁለቱንም ወይም ከሁለቱ አንዱን በመርዳት ለሱዳን መውደምና ለሱዳንውያን እልቂት አስተዋጾ አድርገዋል በማለት ይወቅሳሉ። እየወደመች ካለችው ሱዳንና በጦርነትና ርሀብ እያለቁ ካሉት ሱዳኖች ይልቅ፤ ለአውሮጳውያኑ ዋናው አሳስቢው ጉዳይ ርሀብ ጦርነቱን ሸሽተው ለስደት መንገድ የገቡት ሱዳናውያን ወደ አውሮጳ እንዳያመሩ መሆኑን የአውሮጳ ሕብረት በቅርቡ ለግብጽ የለገሰውን በቢሊዮን የሚቆጠር ገንዘብም ለአብነት ይጠቅሳሉ እነዚሁ ታዛቢዎች።

ቀጣዩን ክፍል ዝለለዉ ስለዚሕ ዝግጅት

ስለዚሕ ዝግጅት

DW-Interview mit Frank-Walter Steinmeier
ምስል DW/R. Oberhammer

ማሕደረ ዜና

ማሕደረ ዜና፣ ኢትዮጵያን ጨምሮ በመላዉ ዓለም የተደረጉ፣ ሊደረጉ የታቀዱና የተነገሩ ዓበይት ፖለቲካዊ ጉዳዮች ዘወትር ሰኞ ይቃኙበታል። ዝግጅቱ የሐገራትን፣ የዓለም አቀፍ እና አካባቢያዊ ማሕበራትን፣ድርጅቶችንና የታዋቂ ግለሰቦችን ያለፈ፣ያሁንና የወደፊት ምግባሮችን እያነሳ በባለሙያዎች አስተያየት የተደገፈ ትንታኔ ይቀርብበታል። አዘጋጅ፣ ነጋሽ መሐመድ